የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ከመርካቶ ዘይት አከፋፋይ ነጋዴዎች ጋር በዘይት አቅርቦት ዙሪያ ተወያዩ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ከመርካቶ ዘይት አከፋፋይ ነጋዴዎች ጋር በዘይት አቅርቦት ዙሪያ ተወያዩ።
ህዳር 20/2018 ዓ ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ከመርካቶ ዘይት አከፋፋይ ነጋዴዎች ጋር በዘይት አቅርቦት ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ በውይይቱ ቢሮው በከተማ ደረጃ የተረጋጋና ጤናማ የንግድ ሥርዓት እንዲጠናከር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀው ያለምክንያት በዘይትም ሆነ በሌሎች ሸቀጦች ላይ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀመር አሳስበዋል።
ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ከውይይቱ በኋላ በአከፋፋዮቹ አማካይነት መጋዘኖችን ተዟዙረው የጎበኙ ሲሆን ከምርት አንፃር በቂ የሆነ የዘይት አቅርቦት መኖሩን አረጋግጠዋል።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments