የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የሮመዳን ወር/ኢድ አል...

image description
- In ንግደረ    0

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የሮመዳን ወር/ኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓል ባዛር በይፋ አሰጀመረ።

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የሮመዳን ወር/ኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓል ባዛር በይፋ አሰጀመረ።

የካቲት 04/2018 ዓ ም

የበዓል ባዛሮቹ በ11ዱም ክ/ከተሞች የተዘጋጁ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ እና ሌሎች የከተማችን ከፍተኛ አመራሮች ባዛሮቹን በይፋ አስጀምረውታል።

በልደታ ክ/ከተማ የተካሄደውን የኢድ አልፈጥር በዓል ባዛሩን መርቀው የከፈቱት ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ባደረጉት ንግግር የከተማ አስተዳደሩ በከተማችን አዲስ አበባ የዋጋ ንረትን ከመከላከል እና የንግድ ስርዓቱን ፍትሃዊነት ከማረጋገጥ አንፃር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ የቻሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን ገልፀዋል።

እንደ ወ/ሮ ሀቢባ ገለፃ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የዕሁድ ገበያዎችን የማስፋፋት ሁለገብ የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት የፍጆታ ምርቶችን እስከ 20 በመቶ ቅናሽ በማቅረብ ገበያውን በዘላቂነት ማረጋጋት ችሏል ብለዋል።

ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ አያይዘውም ቢሮው በየወቅቱ የሚያዘጋጃቸው የበዓል ባዛሮች በበዓል ወቅት ሊከሰት የሚችልን የዋጋ ንረት በመከላከል ገበያውን በማረጋጋት ረገድ የማይተካ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

https://www.facebook.com/profile.php?id=100069351701097

https://t.me/Addisababatradebureau

https://vm.tiktok.com/ZMB4AxNvr/

https://youtube.com/@addisababatradebureau-s2d...

https://x.com/ambomoti32832?s=21

https://www.aacatb.gov.et/


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments