መደበኛ ያልሆነ ንግድ

መደበኛ ያልሆነ ንግድ

image description

እድሳት

  • መደበኛ ባልሆነ ንግድ ሥራ ላይ ለተሰማራ ማንኛውም ሰው የተሰጠውን ደረት ላይ ተንጠልጣይ የሽግግር ጊዜ ፈቃድ ወይም መታወቂያ የበጀት አመት ካበቃ በኋላ ባለው 6 ወራት ጊዜ ውስጥ ማለትም ሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ እስከ ታህሳስ 30 ቀን ድርስ ከግብር አስከፋይ መስሪያ ቤት ክሊራንስ በማቅረብ እና በዚህ ደንብ አንቅፅ 11 ንዑስ አንቅፅ 2 መሠረት ተገቢው ክፍያ ተከፍሎ በየአመቱ በመዝጋቢው አካል መታደስ አለበት።
  • በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 1 በተመለከተው ጊዜ ውስጥ ደረት ላይ ተንጠልጣይ የሽግግር ጊዜ ፈቃድ ወይም መታወቂያውን ሳያድስ የቀረ ሰው በሚቀትሉት ስድስት ወራት ውስጥ ማለትም ከጥር 1 ቀን እስከ ሰኔ 30 ድረስ ባሉት ወራት የመደበኛ የሽግግር ፈቃድ ወይም መታወቂያ ማሳደሻ ክፍያ አጥፍ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ፈቃዱን ማደስ ይቻላል።
  • በዚህ አንቀፅ መሠረት የሽግግር ጊዜ ፈቃድ ወይም መታወቂያውን ያላሳደሰ ሰው ከመዝገብ ይሰረዛል። ተመዝጋቢው የተሰጠውን ደረት ላይ የሚንጠለጠል የሽግግር ጊዜ ፈቃድ ወይም መታወቂያ መመለስ አለበት። ሣይመለስ ቢቀር በእጁ እንዳለ እንደተሰረዘ ይቆጠራል።